በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ብሪታንያ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰየመች


ቦሪስ ጆንሰን
ቦሪስ ጆንሰን

የብሪታንያው ወግ አጥባቂ ፓርቲ ዛሬ ማክሰኞ ይፋ እንዳደረገው፣ ቦሪስ ጆንሰን ምርጫውን በማሸነፋቸው፣ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር እርሳቸው ይሆናሉ።

ቦሪስ ጆንሰን ሰኞ ማታ በተካሄደው የመጀጨረሻ ውድድር፤ ተፎካካሪያቸው የነበሩትን ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጀርሚ ሀንትን በቀላሉ 66% ለ34% በሆነ ብልጫ ነው ያሸነፏቸው።

ባደረጉትም የድል አድራጊነት ንግግር፣ ብሪታንያ እአአ በጥቅምት 31 ከአውሮፓ ሕብረት የምትወጣበትን ቀላል ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ጠቁመው፣ የትምህርቱን፣ የመሠረተ ልማቱንና የፖሊሱን ክፍል ለማሻሻል ሀገራቸው የምታደርጋቸውን ጥረቶች እንደሚያግዙ አመልክተዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG