በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በተቀበረ ፈንጂ ፍንዳታ አምስት ኢትዮጵያውያን ሞቱ


በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር በሚገኘው ገርሁ ሰርናይ በተባለ አካባቢ መንገድ ላይ የተቀበረ ፈንጅ ፈንድቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ በነበረ አምቡላንስ አደጋ ማድረሱን፣ በአደጋውም የአምቡላንሱን አሽከርካሪ ጨምሮ፣ ሁለት ነፍሰ ጡር እናቶችና ሁለት ኃኪሞች በአጠቃላይ የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ዘጋቢያችን ግርማይ ገብሩ የሟች ቤተሰብ አባላትን ጠቅሶ ዘገባ አድርሶናል።

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የትግራይ ቅርንጫፍ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መኮንን አደጋው በተጠቀሰው አካባቢ መድረሱንና በአደጋውም አምስት ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጠዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

በተቀበረ ፈንጂ ፍንዳታ አምስት ኢትዮጵያውያን ሞቱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:53 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG