በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ብሊንከን ከሙሳ ፋኪ ጋር ተወያዩ


የዩናይትድ ስቴትስ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ
የዩናይትድ ስቴትስ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ

ትናንት ከከፍተኛ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው የተወያዩት የዩናይትድ ስቴትስ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ ዛሬ ከአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።

ብሊንከን በትናንት የአዲስ አበባ ቆይታቸው የኢትዮጵያና የዩናይትድ ስቴትስ ግንኙነት ወደ ነበረበት መልካም ሁኔታ ከመመለሱ በፊት መንግሥት ከህወሓት ጋር የደረሰውን የሠላም ሥምምነት በመተግበር ረገድ የተሻለ አፈጻጸም እንዲያሳይ አሳስበዋል።

ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አለመፈጸማችውን ማረጋገጥና ለሁለት ዓመት የተደረገውን ጦርነት ተከትሎ ሁሉን አካታችና ተአማኒነት ያለው የሽግግር ፍትህ ሥርዓት እንዲፈጠር ብሊንከን ጠይቀዋል።

ሁለት አገሮችን ለመጎብኘት ወደ አፍሪካ ያመሩት ብሊንከን የኢትዮጵያ ቆይታቸውን አጠናቀው ዛሬ ወደ ኒዥር አምርተዋል።

XS
SM
MD
LG