በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አንድ ካናዳዊ በኢትዮጵያ የንጹህ ውህ ፕሮጀክትን ለመርዳት የ 12,000 ኪሜ የቢስኪሌት ጉዞ ጀመሩ


በኢትዮጵያ ለሚካሄድ የመጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ገንዘብ ለማሰባሰብ የ 12,000 ኪሎሜትር የቢስክሌት ጉዞ የጀመሩት ካናዳዊ በጎ አድራጊ ማይክል ፖል እስካሁን ባለው ጊዜ ከአንድ ሚልዮን ብር በላይ ማሰባሰባቸውን አስታውቀዋል።

በካናዳ ኤድመንተን የሚኖሩት የ55 አመት እድሜ የሆኑት በጎ አድራጊ ከካይሮ እስከ ኬፕታውን በብስኪሌት በመጓዝ ነው በቦንኬ ኢትዮጵያ ላሉት ሰዎች ንጹህ የመጠጥ ወሀ ለማስገባት የሚደረገውን ጥረት ለመርዳት የወሰኑት። እስካሁን ባለው ጊዜ ከግብጽ ወደ ሱዳን ከሱዳን ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘዋል።

XS
SM
MD
LG