በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቀድሞዋ የተቃዋሚ መሪ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ - በአዲስ አበባ


ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ

"ከመንገድ ተይዛ እንደ ትልቅ የጦር ምርኮኛ እየተንገላታች ነበር ወደ እስር የተወደችው። .. የዛን ጊዜ ይህንኑ ካሜራ የያዙ ጋዜጠኞች ሰለ እርሷ ወንጀል ነበር ዘገባ ለማቅቅረብ ይሯሯጡ የነበረው።" አንጋፋው የመድረክ ሰው ደበበ እሸቱ። "በመጻፍ እና ጥያቄዎች በማንሳታቸው ብቻ አንዳንዶች ለእስር ተዳርገዋል። አሁን ሳይ እናነትም በነጻ ልታናግሩኝ እኔም በነጻ ልናገር ነው፡፡ አዲስ ሆኖብኛል፡፡ ስዕል ብችል ኖሮ በቀለማት ነበር የምገልጸው።" ብርቱካን ሚደቅሳ።

የቀድሞዋ የቅንጅት አመራር አባልና የአንድነት መሪ ወይዘሪት ብርቱካን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ሲደርሱ ሞቅ ያለ አቀባበል ነው የጠበቃቸው።

በራሳቸው አነሳሽነት ሥነ ሥርዓቱን ማዘጋጀታቸውን የገለጹት ወጣቶች “ብርቱካን ገና ከማለዳው ለሌሎች ሕይወት መስመር መያዝ ራሷን ማስቀደም የቻለች መሪ ናት” ይላሉ።

የቀድሞ የቅንጅት አመራር አባል የኪነ ጥበብ ባለ ሞያው አርቲስት ደበበ እሸቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ተገኝተው ወ/ሪት ብርቱካንን ከተቀበሉ ታዋቂ ግለሰቦች አንዱ ነው።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

የቀድሞዋ የተቃዋሚ መሪ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ - በአዲስ አበባ
please wait

No media source currently available

0:00 0:12:01 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG