በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ዲባጢ ወረዳ ውስጥ በዚህ ሳምንት ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን ከነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው መካከል ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ሰዎቹ የታሰሩት መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራቸውና እራሳቸውን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ብለው ከሚጠሩት ታጣቂ ቡድኖች ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መሆኑንም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ "መንግሥት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች እርምጃ ይወስዳል" ካሉ በኋላ በዲባጢም እየታሰሩ ያሉት መንግሥት ጸጥታና መረጋጋትን ለመመለስ የሚወስደው እርምጃ አካል መሆኑን ገልጸው ንጹሃንም ካሉበት እንደሚጣራ አስታውቀዋል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 08, 2023
ንግድ ባንክ በትግራይ እንደገና አገልግሎት መስጠት ጀመረ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
ጆ ባይደን ዓመታዊ ንግግራቸውን ዛሬ ያደርጋሉ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
አቡነ ፍራንሲስ በደቡብ ሱዳን ሰላም እንዲሰፍ ተማፀኑ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
ወደ ትግራይ ክልል የሚወስዱ መንገዶች ጥገና መጠናቀቁ ተገለፀ
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
የደቡብ ክልል ውሳኔ ሕዝብ ውጤት እየተለጠፈ ነው
-
ፌብሩወሪ 07, 2023
- የልብ ጤና ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ቁጥር አንድ ገዳዩ የልብ ደም ስሮች በሽታ