በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ዲባጢ ወረዳ ውስጥ በዚህ ሳምንት ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን ከነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው መካከል ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ሰዎቹ የታሰሩት መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራቸውና እራሳቸውን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ብለው ከሚጠሩት ታጣቂ ቡድኖች ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መሆኑንም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ "መንግሥት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች እርምጃ ይወስዳል" ካሉ በኋላ በዲባጢም እየታሰሩ ያሉት መንግሥት ጸጥታና መረጋጋትን ለመመለስ የሚወስደው እርምጃ አካል መሆኑን ገልጸው ንጹሃንም ካሉበት እንደሚጣራ አስታውቀዋል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ
-
ጁላይ 22, 2024
የነዋሪዎች አስተያየት በፕሬዝደንት ባይደን ውሳኔ ላይ
-
ጁላይ 18, 2024
ጄ. ዲ. ቫንስ “አሜሪካ ትቅደም” መሪ ቃላቸው እንደሆነ አስታወቁ