በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ዲባጢ ወረዳ ውስጥ በዚህ ሳምንት ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን ከነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው መካከል ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ሰዎቹ የታሰሩት መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራቸውና እራሳቸውን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ብለው ከሚጠሩት ታጣቂ ቡድኖች ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መሆኑንም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ "መንግሥት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች እርምጃ ይወስዳል" ካሉ በኋላ በዲባጢም እየታሰሩ ያሉት መንግሥት ጸጥታና መረጋጋትን ለመመለስ የሚወስደው እርምጃ አካል መሆኑን ገልጸው ንጹሃንም ካሉበት እንደሚጣራ አስታውቀዋል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 13, 2025
አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ
-
ማርች 13, 2025
ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች
-
ማርች 13, 2025
የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት
-
ማርች 12, 2025
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ዳግም ተጀመረ