በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዲባጢ ወረዳ ውስጥ 100 ሰዎች መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለፁ


ዲባጢ ወረዳ ውስጥ 100 ሰዎች መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለፁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:53 0:00

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ዲባጢ ወረዳ ውስጥ በዚህ ሳምንት ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን ከነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው መካከል ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ሰዎቹ የታሰሩት መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራቸውና እራሳቸውን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ብለው ከሚጠሩት ታጣቂ ቡድኖች ከመደገፍ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው መሆኑንም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ "መንግሥት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች እርምጃ ይወስዳል" ካሉ በኋላ በዲባጢም እየታሰሩ ያሉት መንግሥት ጸጥታና መረጋጋትን ለመመለስ የሚወስደው እርምጃ አካል መሆኑን ገልጸው ንጹሃንም ካሉበት እንደሚጣራ አስታውቀዋል።

XS
SM
MD
LG