ዋሺንግተን ዲሲ —
በዘጠና ሁለት ዓመት ዕድሜአቸው ማረፋቸው ትናንት የተነገረው የዩናይትድ ስቴትስ የቀድሞዪቱ ቀዳሚት እመቤት ባርብራ ቡሽ አስከሬን ቀብር ከነገ በስተያ ቅዳሜ እንደሚፈፀም ተነግሯል።
ባርብራ ቡሽ
Previous slide
Next slide
የቴክሳሷ ከተማ ህዩስተን የባርብራ ቡሽን ሕይወትና ቅርስ በማክበርና በመዘከር ላይ ስትሆን ትናንት ምሽትና ሌሊቱን የከተማዪቱ ማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ይወድዱት በነበረ ቀለማቸው ሰማያዊ ብርሃን አሸብርቆ እንደነበር ታውቋል።
የሚስ ቡሽ አስከሬን ነገ፤ ዓርብ እርሣቸውና አርባ ሁለተኛው ፕሬዚዳንት ባለቤታቸው ጆርጅ ቡሽ ያዘወትሩባት በነበረ ኤጲስቆጶሳዊት ቤተክርስትያን አርፎ ለሕዝብ ስንብት ክፍት ይሆናል።