በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር የደረሠ ፍንዳታ የሠው ሕይወት አጠፋ


ባህር ዳር
ባህር ዳር

ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር መስቀል አደባባይ በሚገኘው ሚሊኒዬም የወጣቶች ስፖርት ማዕከል ውስጥ ፍንዳታ ደርሶ የሁለት ሰው ሕይወት ማጥፋቱን ቢያንስ አምስት ሠዎች መቁሰላቸውን ከአካባቢው ያነጋገርናቸው ምንጮች ገልፀውታል፡፡

ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር መስቀል አደባባይ በሚገኘው ሚሊኒዬም የወጣቶች ስፖርት ማዕከል ውስጥ ፍንዳታ ደርሶ የሁለት ሰው ሕይወት ማጥፋቱን ቢያንስ አምስት ሠዎች መቁሰላቸውን ከአካባቢው ያነጋገርናቸው ምንጮች ገልፀውታል፡፡

ፍንዳታው የደረሠው ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ሰለተገደሉትና ሰለቆሰሉት ሠዎች ማንነትና ቁጥር ለማጣራት ጥረት ተደርጓል፡፡

ወደ አማራ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ንግሡ ጥላሁን ያደረግነው ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ አልተሳካም፡፡ ጥረታችንን እንቀጥላለን፡፡

ከባህር ዳር ያነጋገሩን ግለሰብ ለደኅንነታቸው ስለሰጉ በጠየቁን መሠረት ድምፃቸውን ቀይረናል፡፡ በኮንሰርቱ ላይ የነበሩትን አርቲስቶች ስም ዝርዝር በመጥቀስ ይጀምራሉ፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር የደረሠ ፍንዳታ የሠው ሕይወት አጠፋ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:17 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG