አዲስ አበባ —
የጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ መንግሥት በድርቅ ለተጎዱ የአፍሪካ ሀገሮች የሚሠጠውን ዕርዳታ ወደ 1.5 ቢሊዮን ዩሮ ከፍ እንደሚያደርግ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታውቀዋል፡፡
ግዙፉን የአፍሪካዊያን ስደት ለማስቆም ደግሞ ሁሉን አቀፍ መፍትኄ እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር አስገንዝበዋል፡፡
ዛሬ ከዕኩለ ቀን በኋላ በአፍሪካ ሕብረት ፅ/ቤት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ የሠጡት የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሚስተር ሙሳ ፋኪ ማማት እና የጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ ምክትል ቻንስለርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲግማር ገብርኤል በአህጉሪቱ በሚታዩ የተለያዩ ችግሮች ላይ እንደተወያዩ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ