በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች ይዞታ

በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች ለወራት ሲማጸኑ ከነበሩበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጽ/ቤት ደጃፍ በኃይል ወደተለያዩ አካባቢዎች መጋዛቸውን የስደተኞቹ ተወካዮች አስታወቁ።

የኃይል እርምጃውን ማምለጣቸውን የተናገሩ ስደተኞች እንዳመለከቱት፥ የየመን ፖሊስ ኃይል ነው፥ በስደተኞች ጽ/ቤት ተመዝግበው ለበርካታ ዓመታት በዚያች አገር የኖሩትን ጨምሮ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩትን እነኚህን ስደተኞች በከፍተኛ የኅዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እያሳፈረ በብዙ መቶ ኪሎሜትሮች ወደ ራቁ አካባቢዎች ያጓጓዘው።


This item is part of
XS
SM
MD
LG