በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ታዋቂዪቱ የተቃዋዊ መሪ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በጊዜያዊነትም ቢሆን ራሳቸውን ከፖለቲካ ማግለላቸውን አስታወቁ።

የሁለት ሺህ ሁለቱ ምርጫ ከተካሄደ ከአራት ወራት በኋላ የተለቀቁት ወይዘሪት ብርቱካን ስለወደፊት አካሄዴ ጊዜዬን ወስጄ ማሰብ አለብኝ፤ ነበር ያሉት ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል።

ባለፈው ሳምንት በተለዋወጡት የሞባይል ቴሌፎን የጽሁፍ መልዕክት (Text) የሰላሳ ስድስት ዓመቷ የአንድነት መሪ ወ/ሪት ብርቱካን የስድስት ዓመትዋን ልጃቸውን ይዘው በቅርቡ ለረጅም ጊዜ ቆይታ ወደዩናይትድ ስቴትስ እንደሚጉዋዙ አረጋግጠዋል።

This item is part of
XS
SM
MD
LG