በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አጣሪ ቡድን ወደ ገንዳ ውኃ ሊላክ ነው


ባህር ዳር
ባህር ዳር

ምዕራብ ጎንደር ውስጥ በገንዳ ውኃ የተፈፀመውን ግድያ የሚያጣራ ቡድን ወደ አካባቢው እንደሚልኩ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አስታወቁ።

ምዕራብ ጎንደር ውስጥ በገንዳ ውኃ የተፈፀመውን ግድያ የሚያጣራ ቡድን ወደ አካባቢው እንደሚልኩ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አስታወቁ።

ርዕሰ-መስተዳድሩ ዛሬ ሰጥተውታል ያለውን መግለጫ ጠቅሶ ፋና ባሠራጨው ዘገባ የአንድ የኮንስትራክሽን ድርጅት መኪኖችን አጅበው ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ የመከላከያ አባላት ጋር በተፈጠረው ግጭት በጉዳዩ ውስጥ ያልነበሩ ሰዎች ጭምር መገደላቸውን መጠቆማቸውን አመልክቷል።

በምዕራብ ጎንደር አካባቢ የእርስ በእርስ መገዳደል እየቀጠለ መሆኑን የተናገሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክልሉ መንግሥት በአካባቢው ሰላም የማስከበር ኃላፊነቱን ለመወጣት ሕጋዊና ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚንቀሳቀስ ማስታወቃቸውን ጠቁሟል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG