በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የደብረ ብርሃን-ደሴ መንገድ ከወር በኋላ ሲከፈት ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ተጠየቀ


የደብረ ብርሃን-ደሴ መንገድ ከወር በኋላ ሲከፈት ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ተጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:22 0:00

የደብረ ብርሃን-ደሴ መንገድ ከወር በኋላ ሲከፈት ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ተጠየቀ

ከአንድ ወር በላይ ተቋርጦ የነበረው የደብረ ብርሃን-ደሴ መንገድ፣ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

መንገዱ በጸጥታ ምክንያት መዘጋቱን ያስታወሰው የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት፣ የአካባቢው ሰላም መሻሻል በማሳየቱና ኅብረተሰቡም እንዲከፈትለት ተደጋጋሚ ጥያቄ በማቅረቡ መንገዱ መከፈቱን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሠሪዎች ፌዴሬሽን በበኩሉ፣ በተከፈተው መሥመር ላይ ዛሬ ስምሪት መጀመሩን ጠቁሟል፡፡

የመንገዱ መዘጋት ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳቶችን ማስከተሉን፣ በሰሜን ሸዋ ዞን የአጣዬ ከተማ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሰንበቴ ከተማ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG