በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢና ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢ ዶሎ ከተሞች ውስጥ በመንግሥት ኃይሎችና የመንግሥት ባለሥልጣናት "ሸኔ" በሚሏቸው፣ እራሳቸውን “የኦሮሞ ነፃነት ጦር” እያሉ በሚጠሩት ታጣቂዎች መካከል ዛሬ የተኩስ ልውውጥ መካሄዱን ቪኦኤ ያነጋገራቸው የከተሞቹ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጋምቤላ ከተማ ውስጥም ከማለዳ ጀምሮ እስከ ረፋድ የቆየ የተኩስ ድምፅ መሰማቱን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ኮምዩኒኬሽንስ ፅህፈት ቤት ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፁ ላይ ባሠፈረው ፅሁፍ "በጋምቤላ ከተማ ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ እርምጃ ተወስዷል" ሲል ብሏል።
የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣናት ደግሞ ጊምቢና ደምቢ ዶሎ ውስጥ ተፈጥረዋል ስለተባሉት ሁኔታዎች መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ግን “የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት” እንደሆነ የሚናገረው ቡድን ዓለምአቀፍ ቃል አቀባይ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ኦዳ ተርቢ ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፃቸው ላይ ባወጡት ፅሁፍ ከጋምቤላ ነፃነት ግንባር ጋር በመሆን ደምቢ ዶሎ ከተማ ላይ የጋራ ዘመቻ እያካሄዱ መሆናቸውን ገልፀል። ናኮር መልካ ዝርዝሩን ይዟል።
/ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ
-
ጁላይ 22, 2024
የነዋሪዎች አስተያየት በፕሬዝደንት ባይደን ውሳኔ ላይ
-
ጁላይ 18, 2024
ጄ. ዲ. ቫንስ “አሜሪካ ትቅደም” መሪ ቃላቸው እንደሆነ አስታወቁ