በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢና ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢ ዶሎ ከተሞች ውስጥ በመንግሥት ኃይሎችና የመንግሥት ባለሥልጣናት "ሸኔ" በሚሏቸው፣ እራሳቸውን “የኦሮሞ ነፃነት ጦር” እያሉ በሚጠሩት ታጣቂዎች መካከል ዛሬ የተኩስ ልውውጥ መካሄዱን ቪኦኤ ያነጋገራቸው የከተሞቹ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጋምቤላ ከተማ ውስጥም ከማለዳ ጀምሮ እስከ ረፋድ የቆየ የተኩስ ድምፅ መሰማቱን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ኮምዩኒኬሽንስ ፅህፈት ቤት ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፁ ላይ ባሠፈረው ፅሁፍ "በጋምቤላ ከተማ ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ እርምጃ ተወስዷል" ሲል ብሏል።
የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣናት ደግሞ ጊምቢና ደምቢ ዶሎ ውስጥ ተፈጥረዋል ስለተባሉት ሁኔታዎች መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ግን “የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት” እንደሆነ የሚናገረው ቡድን ዓለምአቀፍ ቃል አቀባይ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ኦዳ ተርቢ ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፃቸው ላይ ባወጡት ፅሁፍ ከጋምቤላ ነፃነት ግንባር ጋር በመሆን ደምቢ ዶሎ ከተማ ላይ የጋራ ዘመቻ እያካሄዱ መሆናቸውን ገልፀል። ናኮር መልካ ዝርዝሩን ይዟል።
/ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 19, 2025
የኦክላሆማ ግዛት ትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን የኢሚግሬሽን ኹኔታ ለመመዝገብ ዐቅደዋል
-
ፌብሩወሪ 19, 2025
የአውሮፓ መሪዎች በዩክሬንና በአህጉሩ ጸጥታዊ ጉዳዮች ላይ አስቸኳይ ጉባኤ አካሔዱ
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
ስደተኞችን የማባረሩ ሂደት በካሊፎርኒያ የእርሻ ሠራተኞች ላይ ስጋት ፈጥሯል
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
ትግራይ ክልል ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚነት ጥሪ አቀረበ
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
በኬንያ ከግንቦት ወር ወዲህ 82 ሰዎች በግዳጅ ተሰውረዋል - የኬንያ ሰብአዊ መብት ቡድን