በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢና ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢ ዶሎ ከተሞች ውስጥ በመንግሥት ኃይሎችና የመንግሥት ባለሥልጣናት "ሸኔ" በሚሏቸው፣ እራሳቸውን “የኦሮሞ ነፃነት ጦር” እያሉ በሚጠሩት ታጣቂዎች መካከል ዛሬ የተኩስ ልውውጥ መካሄዱን ቪኦኤ ያነጋገራቸው የከተሞቹ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጋምቤላ ከተማ ውስጥም ከማለዳ ጀምሮ እስከ ረፋድ የቆየ የተኩስ ድምፅ መሰማቱን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ኮምዩኒኬሽንስ ፅህፈት ቤት ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፁ ላይ ባሠፈረው ፅሁፍ "በጋምቤላ ከተማ ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ እርምጃ ተወስዷል" ሲል ብሏል።
የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣናት ደግሞ ጊምቢና ደምቢ ዶሎ ውስጥ ተፈጥረዋል ስለተባሉት ሁኔታዎች መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ግን “የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት” እንደሆነ የሚናገረው ቡድን ዓለምአቀፍ ቃል አቀባይ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ኦዳ ተርቢ ዛሬ በማኅበራዊ መገናኛ ገፃቸው ላይ ባወጡት ፅሁፍ ከጋምቤላ ነፃነት ግንባር ጋር በመሆን ደምቢ ዶሎ ከተማ ላይ የጋራ ዘመቻ እያካሄዱ መሆናቸውን ገልፀል። ናኮር መልካ ዝርዝሩን ይዟል።
/ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 13, 2025
አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ
-
ማርች 13, 2025
ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች
-
ማርች 13, 2025
የቀረጡ ጉዳይ በዩናይትድ ስቴትስ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው አለመረጋጋት
-
ማርች 12, 2025
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ዳግም ተጀመረ