በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቡሩንዲ የአባይ ተፋሰስ አገሮችን ስምምነት ፈረመች


ግብጽና ሱዳን የአባይ ወንዝን 98ከመቶ ውሃ ተጠቃሚ ናቸው
ግብጽና ሱዳን የአባይ ወንዝን 98ከመቶ ውሃ ተጠቃሚ ናቸው

የናይል ተፋሰስ አገሮች በአባይ ወንዝ ላይ የሚኖራቸውን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተፈረመውን ስምምነት ቡሩንዲ ስድስተኛ አገር በመሆን ተቀላቀለች።

በ1922ዓም በተፈረመው የአባይ ወንዝ አጠቃቀም ስምምነት ላይ ግብጽና ሱዳን 98ከመቶ የሚሆነውን የአባይ ውሃ በጥቅም ላይ እንዲያውሉ ይፈቅዳል።

የአባይ ተፋሰስ አገሮች የውሃው አጠቃቀም ፍትሃዊ እንዲሆን በመጠየቅ፤ በአንድነት የግብጽን መንግስት ጫና ለመቋቋም ነው ስምምነት በመፈራረም ላይ ያሉት።

ይሄንን ስምምነት ኢትዮጵያ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ዩጋንዳ አስቀድመው የፈረሙት ሲሆን፤ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በጽንሰ-ሀሳቡ ተስማምታ ፊርማዋን እንደምታኖር ቃል ገብታለች።

XS
SM
MD
LG