በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአዲስ አበባ የታክሲ ቀጠና አሰራር በመዲናይቱ የመጓጓዣ እጥረት ፈጠረ


ባለታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ መትተዋል

በአዲስ አበባ ከተማ ተሳፋሪዎችን የሚያመላልሱ (በልማድ ሚኒባስ በመባል የሚታወቁት) ታክሲዎች በተመደበላቸው መስመር ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው የታክሲ አሰራር ሰሞኑን ተግባራዊ ቢደረግም ከቅሬታዎች ነፃ አልሆነም።

ሠሞኑን በከተማይቱ ታዬ የሚባለው የተሽከርካሪ እጥረት እያነጋገረ ባለበት፤ ዘጋቢዎቻችን ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች፥ ተሳፋሪውንና አስከርካሪዎችን በማነጋገርና እንዲሁም የታክሲ ባለንብረቶችንና አዲሱን ህግ ያረቀቀና ተግባራዊነቱን የሚከታተለውን የመንግስት ተቋም ተጠሪ ጨምሮ የሁሉንም ወገኖች ዕይታ ያካተተ ሠፋ ያለ ዘገባ አጠናቅረዋል።

ሰኞለት ሥራ አቁመው የነበሩት ሚኒባስ ታክሲዎች በአብዛኛው ዛሬ ወደ ሥራ እንደተመለሱ የአዲስ አበባ ትራንስፖርትና መንገዶች ቢሮ ባለሥልጣን ሲገልፁ፤ የታክሲ ባለቤቶች ደግሞ አሁንም አሉን የሚሏቸውን ልዩ ልዩ ችግሮች ይዘረዝራሉ።

ዘጋቢዎቻችን እስክንድር ፍሬውና መለስካቸው አምሃ ያጠናቀሩትን ዘገባ ያዳምጡ።

XS
SM
MD
LG