በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አምባሳደር ፍሰሃ አስገዶም ስለፕሬዚዳንት ኢሣያስ ቃለ ምልልስ


ፎቶ ፋይል፦ አምባሳደር ፍሰሀ አስገዶም
ፎቶ ፋይል፦ አምባሳደር ፍሰሀ አስገዶም

የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ከመንግሥታቸው መገናኛ ብዙኃን ጋር ከትናንት በስተያ ቃለ ምልልስ አድርገው በሃገራቸውና በቀጣናው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያን በሚመለክት ካነሷቸው ነጥቦች መካከል "በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የሰላምና የትብብር ሥምምነት ከተፈረመ በኋላ ሰላሙ ያልተዋጠላቸው የህወሃት መሪዎችና ደጋፊዎች ሰላሙን ለማሰናክል ሲሰሩ ነበር። በሰሜን እዝ ላይ እርምጃ የወሰዱትም አዲስ አበባ ያለውን መንግስት ለመገልበጥና ወደ ኤርትራ ለማምራት ነበር" ማለታቸውን ዘግበናል።

ቀደም ሲል እስከ አምባሳደርነት በተለያዩ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ደረጃዎች አገልግለው በጡረታ የተገለሉትና አሁን ሥልጣን ላይ የሌለው "የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ህጋዊ ወኪል ነኝ" ያሉን አምባሳደር ፍሰሀ አስገዶም አስተያየታቸውን እንዲሰጡበት ጋብዘናል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

አምባሳደር ፍሰሃ አስገዶም ስለፕሬዚዳንት ኢሣያስ ቃለ ምልልስ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:11 0:00


XS
SM
MD
LG