አዲስ አበባ —
ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ ማጨስ የሚከለክለውን ሕግ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር መሻሻሎች አሉ ሲል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በተለይ ለአንዳንድ የውጭ ዜጎች አዲስ ነገር እየሆነባቸው ነው፣ በሂደት ግን አየተለመደ ይሄዳል ብለዋል - በሚኒስቴር መሥራቤቱ የፖሊሲ አማካሪ ዳዊት ዲቃሶ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፡፡
በጤና፣ በሥነ ሕዝብና በመድሐኒት ቁጥጥር ላይ የሚመክር የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ በአፍሪካ ሕብረት የስብሰባ አዳራሽ ተጀምሯል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ