በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአፍጋኒስታን በሥህተት የመንግሥት ወታደሮች ተገደሉ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

አፍጋኒስታን በምትገኘው ሄልማንድ ክፍለ-ሃገር ላይ የተካሄደ የውጭ የአየር ድብደባ በሥህተት ቢያንስ 17 የመንግሥት ወታደሮችን ገድሎ 14 አቁስሏል።

አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የፀጥታ ባለሥልጣን በተናግረው መሰረት የአየር ድብበደባው የተካሄደው ከክፍለ-ሀገሩ መዲና ላሽካር ጋህ ወጣ ብሎ በሚገኝ የፖሊስ ኃይሎች ከታሊባን አማፅያን ጋር ይዋጉ በነበረበት ቦታ ላይ ነው።

አተሁላህ አፍጋን የተባሉ ሄልማንድ ያለው የክፍለ-ሀገሩ ምክር ቤት ኃላፊ የአውራ-ጎዳና የፖሊስ ግብረ-ኃይል አዛዥ በስህተት ከተገደሉት መካከል አንዱ መሆናቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG