በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የታሊባን የፖለቲካ ጽሕፈት ቤት ላይ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ደረሰ


የአፍጋኒስታን የጸጥታ ጠባቂ በደቡባዊ አፍጋኒስታን ካንዳሃር ከተማ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ደረሰ ከደረሰበት ሥፍራ ተሽከርካሪዎች ላይ ፍተሻ እያካሄደ እአአ መጋቢት 21/ 2024
የአፍጋኒስታን የጸጥታ ጠባቂ በደቡባዊ አፍጋኒስታን ካንዳሃር ከተማ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ደረሰ ከደረሰበት ሥፍራ ተሽከርካሪዎች ላይ ፍተሻ እያካሄደ እአአ መጋቢት 21/ 2024

ደቡባዊ አፍጋኒስታን ካንዳሃር ከተማ ውስጥ በሚገኝ የታሊባን የፖለቲካ ጉዳዮች ዋና ጽሕፈት ቤት ላይ ዛሬ ሐሙስ ማለዳ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት ቢያንስ ሦስት ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ በአሁኑ ወቅት ያልተለመደ በሆነው ጥቃት ከአስር የሚበልጡ ሌሎች ሰዎች መቁሰላቸው ታዉቋል፡፡

የታሊባን ባለሥልጣናት በሰጡት ቃል አጥፍቶ ጠፊው በላዩ የታጠቀውን ቦምብ ያፈነዳው ደሞዝ የሚቀበሉ ሰዎች በአዲሲቱ ካቡል ባንክ ደጃፍ ተሰልፈው እየተጠባበቁ ሳሉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለጥቃቱ እስካሁን ኃላፊ ነኝ ያለ ወገን የለም፡፡ በአደባባይ የማይታዩት የታሊባን ከፍተኛ መሪ ሂባቱላ አኽሁንዛዳ የሚኖሩት አክራሪው ቡድን በተመሰረተባት ካንዳሃር ሲሆን አፍጋኒስታንን በሙሉ የሚያስተዳድሩት እዚያው ሆነው ነው፡፡ ወንዶች ብቻ ያሉበት ካቡል የሚገኘው የታሊባን መንግሥት ሥራው ከከተማዋ ብዙም የማይወጡት አኹንዳዛ ከካንዳሃር በየጊዜው የሚያስተላልፉትን አዋጅ ተግባራዊ ማድረግ ብቻ ነው፡፡

የታሊባኑ መሪ ልጃገረዶች ከስድስተኛ ክፍል በላይ ትምህርት እንዳይማሩ እንዲሁም ሴቶች በመንግሥትም ሆነ በግል ድርጅቶች አንዳይሰሩ መከልከላቸው ይታወሳል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG