በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የደቡብ ሱዳን የቀድሞ ባለሥልጣናት ያዲሳባ መግለጫ


ጁባ ውስጥ እሥር ላይ የነበሩት ከናይሮቢ አዲስ አበባ የገቡት የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት
ጁባ ውስጥ እሥር ላይ የነበሩት ከናይሮቢ አዲስ አበባ የገቡት የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት

በምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮቹ የጋራ ልማት ባለሥልጣን - ኢጋድ አማካኝነት በሚካሄደው ድርድር ለመሳተፍ አዲስ አበባ የገቡት ሰባት ከእሥር የተፈቱ የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተቀሩት አራት እሥረኞችም እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።


የተቃዋሚዎቹ ዋና ተደራዳሪ ታባን ዴንግ ጋይ እና የደቡብ ሱዳን መንግሥት ዋና ተደራዳሪ ንሂያል ዴንግ ንሂያል
የተቃዋሚዎቹ ዋና ተደራዳሪ ታባን ዴንግ ጋይ እና የደቡብ ሱዳን መንግሥት ዋና ተደራዳሪ ንሂያል ዴንግ ንሂያል

please wait

No media source currently available

0:00 0:04:18 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

በምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮቹ የጋራ ልማት ባለሥልጣን - ኢጋድ አማካኝነት በሚካሄደው ድርድር ለመሳተፍ አዲስ አበባ የገቡት ሰባት ከእሥር የተፈቱ የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተቀሩት አራት እሥረኞችም እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።

በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል መግለጫ የሰጡት ሰባቱ ሰዎች እስካለፈው ታኅሣስ አጋማሽ ድረስ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት የነበሩ ናቸው፡፡

የፍትህ ሚኒስትር፣ የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የቴሌኮምዩኒኬሽንስ ሚኒስትር እና ሌሎችም ይገኙባቸዋል፡፡

ተፈናቃዮችና ሁከት የሸሹ በጁባ ዓለምአቀፍ አይሮፕላን ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኘው የኡንሚስ ግቢ - ማክሰኞ፣ ታኅሣስ 8/2006 ዓ.ም /ፎቶ - ፋይል/
ተፈናቃዮችና ሁከት የሸሹ በጁባ ዓለምአቀፍ አይሮፕላን ጣቢያ አቅራቢያ በሚገኘው የኡንሚስ ግቢ - ማክሰኞ፣ ታኅሣስ 8/2006 ዓ.ም /ፎቶ - ፋይል/
የመፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ አድርጋችኋል በሚል ካለፈው ታኅሣስ 7/2006 ዓ.ም ጀምሮ በእሥር ላይ ቆይተው በምሥራቅ አፍሪካው በይነ-መንግሥታዊ የልማት ባለሥልጣን አማካይነት የተካሄደውን ድርድር ተከትሎ ከእሥር የተፈቱት በቅርቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ናይሮቢ ላይ ጥቂት ቆይታ አድርገው ትናንት፤ የካቲት 5/2006 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

የቀድሞዎቹ የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት በዛሬው መግለጫቸው የአራቱ ታሣሪዎች መፈታት “በቀጣይነት ለሚካሄደው ድርድር ቁልፍ ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡

በድርድሮቹ ውስጥም ከእንግዲህ የሚሣተፉት እንደ ሦስተኛ ወገን እራሣቸውን ችለው መሆኑንም ተናግረዋል።

የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG