አዲስ አበባ —
የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ
ከ50 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያለውና 29 ቢሊዮን ብር ወጭ የሚደረግበት የአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡ የከተማዋን ገፅታ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀይር የተገለፀው ፕሮጀክት ይፋ እንደሚያደርጉ የተጠበቁት ጠ/ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ግን በሥነ ስርዓቱ ላይ አልተገኙም፡፡
እሳቸውን በመወከል ጭምር ፕሮጀክቱን ያስጀመሩት፣ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ ጠ/ሚኒስትሩ ያልተገኙት በአስቸኳይ ሥራ ስለተያዙ ነው ብለዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
-
እስክንድር ፍሬው