በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሴኔጋል ምርጫ ማኪ ሳል አሸነፉ


ፎቶ ፋይል፦ ከድምፅ መስጫ የምርጫ ጣቢያዎች የተሰበሰቡ ሳጥኖች ዳካር፣ ሴኔጋል እአአ 8/4/2022
ፎቶ ፋይል፦ ከድምፅ መስጫ የምርጫ ጣቢያዎች የተሰበሰቡ ሳጥኖች ዳካር፣ ሴኔጋል እአአ 8/4/2022

የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ጥምረት ባለፈው ወር በተካሄደው የህዝብ እንደራሴዎች ምርጫ በጠባብ ልዩነት ማሸነፉን ኤኤፍፒ ዘግቧል።

በአዲሱ ቅንጅታቸው ምክንያትም በፓርላማው ውስጥ ፍፁም የበላይነት ይዘው እንደሚቀጥሉ ታውቋል።

“የሪፐብሊኳ ቅንጅት” ወይም በምኅፃር ኤአርፒ የሚባለውን የራሳቸውን ፓርቲ ጨምሮ ሌሎችንም ያቀፈው የፕሬዚዳንቱ ጥምረት ፓርላማው ካሉት 165 መቀመጫዎች 82ቱን ማሸነፉን የሴኔጋል ከፍተኛው ፍርድ ቤት የሆነው የሆነው ህገመንግሥታዊ ችሎት ትናንት፤ ሃሙስ አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG