በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የምዕራብ አፍሪቃ ልዑካን ከማሊ የመፈንቅለ መንግስት መሪዎች ጋር ተነጋገሩ


የማሊ መፈንቅለ-መንግስት
የማሊ መፈንቅለ-መንግስት

በቀድሞው የናይጀርያ መሪ ጉድላክ ጆናታን የሚመሩት የምዕራብ አፍሪቃ ልዑካን ትላንት ሌሊት በማሊ መዲና ባማኮ መፈንቅለ መንግስት ካካሄዱት ወታደሮች ጋር ተገናኝተው ከተነግገሩ በሁዋላ ብሩህ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ወታደሮቹ በያዝነው ሳምንት የሀገሪቱ ፕረዚዳንት ቡባካር ከይታ ከስልጣን እንዲወርዱና መንግስታቸውን እንዲበትኑ ማስገደዳቸው ያሚታወቅ ነው።

አጃንስ ፍራንስ ፕረስ የዜና አገልግሎት በዘገበው መሰረት ቃለ-መጠይቁ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው ሲሉ ጆናታን ትላንት ማታ ተናግረዋል።

የምዕራብ አፍሪቃ ሀገሮች የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ECOWAS መልእክተኞች ከስልጣን ከተወገዱት ፕረዚዳንትና በወታደሮቹ ከተያዙት ሌሎች የመንግስትና ወታደራዊ ባለስልጣኖች ጋርም እንደተነጋገሩ ታውቋል።

“ፕረዚዳንት ከይታን አይተናቸዋል። በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት” ሲሉ ጆናታን መናገራቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘግቧል።

የወታደሮቹ ቃል አቀባይ ኢስማየል ዋጉም ንግግሮቹ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄዱ ነው ከሚለው ጋር መስማማታቸው ተገልጿል።

መልእክተኞቹ ማሊ የሄዱት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ተወላጆች መፈንቅለ መንግስት ያካሄዱትን ወታደሮች ለመደገፍ ሰልፍ ባደረጉበት ማግስት ነው።

XS
SM
MD
LG