በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከሊቢያ የተነሳው ጀልባ 483 ፍልሰተኞችን ይዞ ነበር


ከ400 በላይ ፍልሰተኞችን ያሳፈራ ጀልባ በቀርጤስ ደሴት የግሪክ የባህር ጠረፍ ሲደርስ የነፍስ አድን ሰራተኞች በአካባቤው ደርሰው እአአ 3/22/2022
ከ400 በላይ ፍልሰተኞችን ያሳፈራ ጀልባ በቀርጤስ ደሴት የግሪክ የባህር ጠረፍ ሲደርስ የነፍስ አድን ሰራተኞች በአካባቤው ደርሰው እአአ 3/22/2022

በቅርቡ ከሊቢያ የተነሳውና በሜዲትሬኒያን ባህር ላይ ከመስመትጥ የዳነው የወላለቀ ጀልባ 483 ሰዎችን ጭኖ እንደነበር የግሪክ ባለሥልጣናት ዛሬ አስታውቀዋል።

በአደገኛ ማዕበል ውስጥ ሆኖ መቅዘፍ ያልቻለውን ጀልባ የባህር ላይ ድንበር ጠባቂዎች ጎትተው ወደ ዳር ሲያወጡት፣ 25 ሜትር በሚሆነው ጀልባ ላይ 336 ወንዶች፣ 10 ሴቶ እና 128 ሴትና ወንድ ልጆች ተጨናንቀው ተሳፍረውበት እንደነበር ታውቋል።

እንደ አሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ በደቡብ ግሪክ በምትገኘው ክሪት ደሴት አቅራቢያ ሲቀዝፉ የድረሱልን ጥሪ በማስተላለፋቸው ከመስመጥ ሊተርፉ ችለዋል።

የግሪክ የስደተኞች ሚኒስትር የሆኑት ኖቲስ ሚታራቺ ፍልሰተኞቹ ወደ አውሮፓ ኅብረት አገራት እንዲዛወሩ በመጠየቅ ለኮሚሽኑ ማክሰኞ ዕለት ደብዳቤ ጽፈዋል።

XS
SM
MD
LG