በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በግሪክ ሁለት ባቡሮች ተጋጭተው 36 ሰዎች ሞቱ


በሰሜን ግሪክ አንድ የመንገደኞች መጓጓዣና ሌላ የጭነት ባቡር ዛሬ ተጋጭተው እስከ አሁን 36 ሰዎች ሲሞቱ 85 ቆስለዋል፡፡
በሰሜን ግሪክ አንድ የመንገደኞች መጓጓዣና ሌላ የጭነት ባቡር ዛሬ ተጋጭተው እስከ አሁን 36 ሰዎች ሲሞቱ 85 ቆስለዋል፡፡

በሰሜን ግሪክ አንድ የመንገደኞች መጓጓዣና ሌላ የጭነት ባቡር ዛሬ ተጋጭተው እስከ አሁን 36 ሰዎች ሲሞቱ 85 ቆስለዋል፡፡

በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዙ የነበሩት ሁለቱ ባቡሮች የተጋጩት ከመዲናዋ አቴንስ 380 ኪ.ሜ. ላይ ቴምፔ ሲሆን፣ ቢያንስ ሶስት ፉርጎዎች በእሳት ተቀጣጥለዋል፡፡

350 መንገደኞችን ከያዘው ባቡር ውስጥ፣ 250 የሚሆኑት መንገደኞች ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ወይም አነስተኛ ጉዳት እንደገጠማቸው ታውቋል፡፡

የአደጋ ሠራተኞች ፍርስራሹ ውስጥ ተቀብረው ሊኖሩ የሚችሉ ሰዎችን ለማዳን በመረባረብ ላይ ናቸው፡፡

66 ሰዎች ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ፣ ስድስቱ በጽኑ የተጎዱ መሆናቸውን የግሪክ እሳት አደጋ አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ሁለቱ ባቡሮች ክፉኛ በመጋጨታቸው የአደጋ ሠራተኞቹን ሥራ ከባድ እንዳደረገው የእሳት አደጋ አገልግሎት ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡

XS
SM
MD
LG