አዲስ አበባ —
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ከ3.8 ሚሊዮን የማያንስ ህዝብ ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆነ ሰብዓዊ እርዳታ እየደረሰው መሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በክልሉ በየትኛውም ክፍል ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ ክፍት ቢሆንም የዓለም አቀፍ ተዋናይ ድርሻ ግን ከ30 በመቶ አላለፈም ሲል ሚኒስትሩ ገለጸ።
የሕዳሴው ግድብ ድርድር ወደፊትም በአፍሪካ ሕብረት አማካኝነት መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ መንግሥት አቋም እንደሆነም ሚኒስትሩ አስታውቋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።