ዋሺንግተን ዲሲ —
ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጀርመኗ ቻንስለር አንጌላ መርክል ጋር በስልክ መወያየታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ጠቆሙ።
ኮቪድ-19ን ለመከላከልና ሥርጭቱን በመግታት ላይ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸው፤ ሀገሪቱ ለኢትዮጵያ ስለለገሰችው የኮቪድ-19 መመርመሪያ ግብዓትና መገልገያ ቁሳቁሶች፤ በዚህ ፈታኝ ወቅትም ጀርመን ከኢትዮጵያ ጎን ለመቆም ያላትን ቁርጠኝነት እና አጋርነት ማሳየቷን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ ማመስገናቸውን ጠቅሰው የሀገር ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የጀርመን ቻንስለር አንጌላ መርክል የታላቁን የኅዳሴ ግድብ አስመልከቶ ለሁሉም አካላት የሚያመች ሥምምነት ላይ ለመድረስ የሚደረጉ ጥረቶችን እንደሚደግፉም በውይይታቸው ገልፀዋል።
አስተያየቶችን ይዩ (2)
ተጨማሪ አስተያየቶችን ለመመልከት ይጫኑ