ባህር ዳር —
በአማራ ክልል ህወሓት ተቆጣጥሯቸው በነበሩ አካባቢዎች በርካታ የፍትህ ተቋማት መውደማቸውን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታውቋል።
ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ የነበረና የፍርድ ሂደታቸው የተጠናቀቁ ፋይሎች በመጥፋታቸው በፍትህ ሥርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር የጠቆሙት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አቡየ ካሳሁን የጠፉ መዛግብትን በተመለከተ ተመሳሳይ ችግር ውስጥ ገብተው ከነበሩ ሀገሮች ተሞክሮ የሚወስዱ መሆኑን ጠቁመዋል።