መጋቢት፥ የዓለም አቀፍ ሴቶች ወር ነው። ሴቶች ትምህርትንና ሥራን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች እኩል ዕድል እንዲያገኙ ለማብቃት በመላ ዓለም የሚደረጉ ጥረቶች፦ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በጦርነት እና በሌሎችም ሰው ሠራሽ ምክንያቶች መጓተታቸውን፣ በሴቶች ላይ አተኩረው የሚሠሩ ተቋማት ያወጧቸው ሪፖርቶች ያሳያሉ።
ዘንድሮም፣ ወርኃ መጋቢት(ማርች 8)፥ “ትግበራን ማፋጠን” በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም እየታሰበ ይገኛል።
በዐዲስ አበባ የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ኬኔዲ አባተ፣ በርእሰ መዲናዪቱ ጎዳናዎች ላይ ተዘዋውሮ፤ ለመኾኑ የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? የሴቶች እኩልነት እንዲሰፍን ምን ቢደረግ ይበጃል? በማለት ጠይቆ ያገኘውን ምላሽ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።