ታጣቂዎች ወላጆቿን እና ወንድሟን ታጣቂዎች የገደሉባት የ14 ዓመቷ ጌስማ ፤ ገና በለጋ እድሜዋ ታናናሽ ወንድሞቿን እና እህቶቿን የመንከባከብ ኃላፊነት ተረክባለች፤ ጥቃቶቹን ሸሽታ ዳርፉር የሚገኘውን ቀያቸውን ጥላ ለመኮብለል ተገድዳለች። አሁን ቻድ ውስጥ ባለ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ የምትኖረው ጌስማ ቤተሰቧን ለመመገብ ለረዥም ሰዓታት ትሰራለች።
ይህም እውነታ በዳርፉሩ አሰቃቂ ጥቃት ከቀያቸው የተፈናቀሉ አያሌ ታዳጊ ልጆች ዕጣ ሆኗል።
ሄንሪ ዊልኪንስ ያደረሰንን ዘገባ ዝርዝር አሉላ ከበደ እንደሚከተለው ያቀርበዋል።
መድረክ / ፎረም