በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዩክሬይን  ከካርኪቭ ክፍለ ግዛት ከተማ ነዋሪዎች በማስወጣት ላይ ነች


በጎ ፈቃደኞች ከኩፒያንስክ የተፈናቀሉ አረጋውያንን እየረዱ በካርኪቭ፣ ዩክሬን፣ እአአ 17/2024
በጎ ፈቃደኞች ከኩፒያንስክ የተፈናቀሉ አረጋውያንን እየረዱ በካርኪቭ፣ ዩክሬን፣ እአአ 17/2024

ዩክሬይን ከሩሲያ አስለቅቃ ከተቆጣጠረቻት ከሰሜን ምስራቃዊዋ የካርኪቭ ከተማ በብዙ ሺዎች የተቆጠሩ ነዋሪዎችን በማስወጣት ላይ መሆኗን ዛሬ ዓርብ ገለጸች።

ዩክሬይን ሩሲያ ወረራውን ከከፈተችባት ከስድስት ወራት በኋላ ካርኪቭን አስለቅቃ ተቆጣጥራታለች።

በሰሜን ምስራቅ ካርኪቭ ክፍለ ግዛት የምትገኘው ቁልፍ የባቡር መስመር ከተማ ኩፒያንስክ ባለፉት ጥቂት ወራት በሞስኮ ኅይሎች በመድፍ እየተደበደበች ስትሆን የሞስኮ ኅይሎች ከከተማዋ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

የክፍለ ግዛቷ አስተዳዳሪ ያለማቋረጥ በሚደርሰው ድብደባ የተነሳ ለከተማዋ "የኤሊክትሪክም ሆነ የውሃ አቅርቦት ዋስትና ልንሰጥ አንችልም" በማለት ማክሰኞ እለት አስጠንቅቀው ነበር።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG