በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያ ከ9 ሺህ በላይ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታቸው ተገለፀ


የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት
የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት
በኢትዮጵያ ከ9 ሺህ በላይ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ማግኘታቸው ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:22 0:00

ባለፉት 6 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኙ 10 ሺህ የሚጠጉ ስደተኞች ፋይዳ የተሰኘ ዲጂታል መታወቂያ እነደተሰጣቸው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር፣ በምህጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር አስታውቋል።

ዲጂታል መታወቂያው፣ ስደተኞች የተለያዩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የደኅንነት አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እንደሚያስችል ተቋሙ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰማኮ) ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ፣ተመዝግበው እውቅና ማግኘት አለመቻል በተለይ የከተማ ስደተኞችን ለእስር እና መሰል ችግሮች አጋልጧል ሲሉ በቅርቡ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በሂደቱ ላይ መዘግየት መታየቱን የገለፁት በኢትዮጵያ መንግሥት የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኛች ከለላ ዳይሬክተር ዳባ ለሜሳ፣ ለዚህ ምክንያቱ የባለሙያዎች እጥረት እንደሆነ ጠቁመዋል ፡፡ በአሁኑ ወቅት ችግሩን ለመቅረፍ ከዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ጋራ በመተባበር፣ አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎች ሰልጥነው በየካምፖች እንዲሰማሩ ማድረጋቸውንም አስረድተዋል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG