በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአሜሪካ ምርጫ የትውልደ ኢትዮጵያ ድምጽ ሰጪዎች ዕይታ


በአሜሪካ ምርጫ የትውልደ ኢትዮጵያ ድምጽ ሰጪዎች ዕይታ
please wait

No media source currently available

0:00 0:12:19 0:00

ለአራት ቀናት የተከናወነው የዲሞክራቲክ ፓርቲው ብሔራዊ ጉባኤ ትላንት ሐሙስ ምሽት ተጠናቋል።

ፓርቲው ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሄሪስን ለፕሬዝደንትነት፣ የሜንሶታው አገረ ገዥ ቲም ዎልዝን ደግሞ ለምክትል ፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ አቅርቧል።

የሪፐብሊካኑ ፓርቲ ብሔራዊ ጉባኤ ባለፈው ሐምሌ እንዲሁ ተከናውኗል። ዶናልድ ትረምፕንና ጄ ዲ ቫንስን ፓርቲውን ወክለው ለፕሬዝደንትነትና ለምክትል ፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ አቅርቧል።

ሁለቱ ወገኖች ዋይት ሃውስን ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ጥረት የምርጫ ዘመቻቸውን አጡጡፈው የሚቀጥሉበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የምርጫ ክርክሮችም ቀነ ቀጠሮ ተቆርጦላቸዋል።

የሁለቱንም ፓርቲዎች ጉባኤ እና የዘመቻ አካሄድ በተመለከተ በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምን ያስባሉ?

ባልደረባችን እንግዱ ወልዴ የሁለቱም ፓርቲዎች ደጋፊ የሆኑ ድምፅ ሰጪ ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አነጋግሮ ተከታዩን አዘጋጅቷል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG