በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሰሀላ ሰየምት ወረዳ በአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት ሕመም አምስት ሰዎች መሞታቸውን ዞኑ አስታወቀ


የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምርያ
የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምርያ

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞንበሰሀላ ሰየምት ወረዳ ሦስት ቀበሌዎች በተከሠተው አጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት፣ ባለፈው ሳምንት ብቻ አምስት ሰዎች ሲሞቱ፣ 262ቱ ደግሞ በጽኑ መታመማቸውን፣ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ገልጸዋል።

በሰሀላ ሰየምት ወረዳ በአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት ሕመም አምስት ሰዎች መሞታቸውን ዞኑ አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:02 0:00

ለተጨማሪ ምርመራ፣ ናሙና ወደ ክልሉ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለመላክ በዝግጅት ላይ መኾኑን የጠቆሙት ኃላፊው፣ የሕመሙን መስፋፋት ለመቆጣጠር ድጋፍ ሰጭ የሐኪሞች ቡድን ወደ ስፍራው ተልኮ የመከላከል ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል።

በወረዳው የቢላዛ ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ማለደ ብሬ በበኩላቸው፣ በቀበሌው አራት ሰዎች መሞታቸውንና በርካታ ሰዎች ታመው መተኛታቸውን አመልክተዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG