በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከወራት አለመረጋጋት በኃላ ሴኔጋል ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አከናወነች


ከወራት አለመረጋጋት በኃላ ሴኔጋል ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አከናወነች።
ከወራት አለመረጋጋት በኃላ ሴኔጋል ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አከናወነች።

ከወራት አለመረጋጋት በኃላ ሴኔጋል በከፍተኛ ፉክክር የታጀበ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በዛሬ ዕለት አድርጋለች ። በቅርብ ዓመታት ውስጥ በርካታ መፈንቅለ መንግስታትን ባስተናገደው ቀጠና የረጋ ዴሞክራሲ ባህልን ስለ ማስፈኗ የሚነገርላትን ምዕራብ አፍሪካዊት ሀገር መልካም ስም በቅርበ ወራት የታየው አለመረጋጋት ፈትኗል ።

የአሁኑ ምርጫ የተካሄደው ፕሬዚደንት ማኪ ሳል እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ምርጫውን ለማዘገየት ካደረጉት ያልተሳካ ጥረት ከሳምንታት በኃላ ነው ። ሳል በህገ መንግስቱ በተቀመጠው ገደብ መሰረት ለሶስተኛ ጊዜ እንዳይወዳደሩ ታግደዋል ።

የአሁኑ ምርጫ ሴኔጋል በ1960 ከፈረንሳይ ነጻነቷን ካገኘች ወዲህ የተደረገ አራተኛው ዴሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ።

ቀደም ያለው የምርጫ ሂደት ግን በግጨት እና አለመረጋጋት የታወከ እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ለእስራት የተዳረጉበት ስለመሆኑም ተነግሯል ።

በአሁኑ ምርጫ ፉክክር በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ዕጩን ጨምሮ 19 ዕጩዎች ይወዳዳራሉ ። በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ ፉክክር የታየበት ስለመሆኑ በተነገረለት በዚህ ምርጫ ከ50 በመቶ በላይ የህዝብ ድምጽ የሚያገኝ ዕጩ እንደማይኖር ተንታኞች ግምታቸውን አስቀምጠዋል ። በዚህም መሰረት የድጋሚ ምርጫ ይደረጋል የሚለው ግምት አይሏል ። ከዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አማዶ ባ እና ዕውቁ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ኦስማኒ ሶንኮ የሚደግፏቸው ባሲሮ ዲኦማዬ ይገኙበታል(AP)።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG