በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በመርከብ ጠለፋ ወንጀል የተጠረጠሩ 35 ሶማሊያውያን በህንድ ፍርድቤት ሊቀርቡ ነው


በመርከብ ላይ ጥቃት በማድረስ የተጠረጠሩ ሶማሊያዊ ዘራፊዎች ለህንድ ፖሊስ ተላልፈው ሲሰጡ - መጋቢት 23፣ 2024
በመርከብ ላይ ጥቃት በማድረስ የተጠረጠሩ ሶማሊያዊ ዘራፊዎች ለህንድ ፖሊስ ተላልፈው ሲሰጡ - መጋቢት 23፣ 2024


ህንድ የጭነት መርከብ በመጥለፍ የተጠረጠሩ 35 የሶማሊያ የባህር ላይ ዘራፊዎችን ቅዳሜ እለት ወደ ሞምባይ አምጥታለች። ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት፣ የባህር ላይ ኮማንዶዎች የጠለፋ አደጋ የደረሰበትን የጭነት መርከብ መልሰው ከተቆጣጠሩ እና በርካታ ታጋቾችን ካዳኑ በኃላ ነው።

በታህሳስ ወር ጠለፋ የተካሄደበትን መርከብ ህንድ ከአራት ወር በኃላ ያዳነችው ከሶማሊያ የባህር ዳርቻ 480 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ስፍራ ላይ ነው። መርከቧን የማዳኑን ዘመቻ የመራው የህንድ የባህር ኃይል ባወጣው መግለጫ "ዘመቻው የዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎችን በተከተለ እና በቀጠናው የባህር ላይ ጸጥታ እና ደህንነትን ባረጋገጠ መልኩ መከናወኑን" አመልክቷል።

በጠለፋ ወንጀል የተጠረጠሩት ግለሰቦች ቅዳሜ እለት ለፖሊስ ተላልፈው መሰጠታቸውንም አስታውቋል።

በህንድ ፀረ-የባህር ላይ ውንብድና ሕግ መሰረት፣ ዘራፊዎቹ ሰው በመግደል ወይም የመግደል ሙከራ ጥፋተኛ ሆነው ተገኙ የሞት ፍርድ የሚፈረድባቸው ሲሆን፣ በባህር ላይ ዘረፋ ወንጀል ደግሞ የእድሜ ልክ እስራት ይጠብቃቸዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG