በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ደቡብ አፍሪካ እስራኤልን በዘር ማጥፋት ወንጀል በመንግስታቱ ፍ/ቤት ከሰሰች


ሔግ 2016
ሔግ 2016

ደቡብ አፍሪካ እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማውያን ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈፅማለች የሚል ክስ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረበች ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱ እስራኤል ጥቃቷን እንድታቆም ትእዛዝ እንዲሰጥ በትላንትናው ዕለት ጠይቃለች።

ደቡብ አፍሪካ ለዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ያቀረበችው ክስ “በእስራኤል የሚፈጸሙ ድርጊቶች እና ግድፈቶች... በባህሪያቸው የዘር ማጥፋት ወንጀል ናቸው” የሚል ሲሆን እስራኤል ቁርጠኛ የሆነ ዓላማ በመያዝ “በጋዛ ውስጥ የሚገኙ ፍልስጤማውያንን በማጥፋት በሰፊው የፍልስጤም ብሄራዊ፣ ዘር እና ጎሳ የማጥፋት እቅድ እየተገበረች ነው" ብላለች።

ክሱ በተጨማሪም ተቀማጭነቱ በሄግ የሆነውን ፍ/ቤት እስራኤል ጥቃቷን እንድታቆም የአስቸኳይ ጊዜያዊ ማዘዣ እንዲያወጣ ጠይቋል።

ደቡብ አፍሪካ እሷም ሆኑ እስራኤል የጉባኤው ፈራሚዎች በመሆናቸው ጉዳዩን በዘር ማጥፋት ኮንቬንሽን ስር ልትወስደው ትችላለች።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG