በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፓስፖርት የሚጠባበቁ አመልካቾች በሙሉ ፈጥነው ይስተናገዳሉ ሲል ተቋሙ አስታወቀ


ፓስፖርት የሚጠባበቁ አመልካቾች በሙሉ ፈጥነው ይስተናገዳሉ ሲል ተቋሙ አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:22 0:00

ፓስፖርት የሚጠባበቁ አመልካቾች በሙሉ ፈጥነው ይስተናገዳሉ ሲል ተቋሙ አስታወቀ

የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ጠይቀው እየተጠባበቁ ያሉ አመልካቾችን፣ እስከ ታኅሣሥ ወር ድረስ ሙሉ በሙሉ እንደሚያስተናግድ የኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት አስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ፣ የፓስፖርት አገልግሎት ማግኘት እጅግ ከባድ እንደኾነ፣ የሰነዱ ፈላጊዎች እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ፣ ባለፉት ሦስት ወራት ውስጥ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት ታትሞ ወደ ሀገር ውስጥ እንደገባ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዲሬክተር ሰላማዊት ዳዊት አስታውቀዋል፡፡

ዳይሬክተሯ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ የፓስፖርት አገልግሎት በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ሁሉም ዜጎች እስከ ቀጣዩ ታኅሣሥ ወር ድረስ አገልግሎቱን ያገኛሉ፤ ብለዋል፡፡

በሙስና እና በብልሹ አሠራር የተጠረጠሩ 53 የተቋሙ ሠራተኞች እና ደላሎች፣ በቁጥጥር ሥር ውለው ጉዳያቸው እየታየ እንደኾነም፣ ዲሬክተሯ ተናግረዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG