በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢቫንካ ትረምፕ ፍርድ ቤት ቀርበው መሰከሩ


የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልጅ፣ ኢቫንካ ትራምፕ፣ የትራምፕ የንግድ ተቋም የሲቪል ማጭበርበር ችሎት በኒውዮርክ ጠቅላይ ፍርድቤት ተገኝተው ታድመዋል - ህዳር 8፣ 2023
የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልጅ፣ ኢቫንካ ትራምፕ፣ የትራምፕ የንግድ ተቋም የሲቪል ማጭበርበር ችሎት በኒውዮርክ ጠቅላይ ፍርድቤት ተገኝተው ታድመዋል - ህዳር 8፣ 2023

በኒውዮርክ የሲቪል ማጭበርበር ችሎት ትናንት ረቡዕ ፍርድ ቤት የቀረቡት የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት የዶናልድ ትረምፕ ሴት ልጅ ኢቫንካ ትረምፕ፣ ግዙፉን የአባታቸውን የንግድ ተቋም (ኢምፓየር) አደጋ ላይ የጣለውን የሪል ስቴት ስምምነቶችን ዝርዝር መረጃ አላታውስም ሲሉ መስክረዋል።

ባለፈው ሳምንት ምስክርነታቸውን እንደሰጡት ልክ እንደ ወንድሞቻቸው ዶናልድ ትረምፕ እና ኤሪክ ትረምፕ ፣ ኢቫንካ ትረምፕም፣ አጠራጣሪ ከሆነውና ወሳኙን የፍርድ ሂደት የሚመለከቱ ዳኛ ማጭበርበር ተፈጽሟል ካሉበት የግምገማ ዘዴ፣ ራሳቸውን ማራቅ የፈለጉ መምሰላቸው ተነግሯል፡፡

የኒውዮርክ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሌቲሺያ ጀምስ ያቀረቡት ክስ ዶናልድ ትረምፕ በቀላሉ ብድር እና ኢንሹራንስ ለማግኘት የሀብት እሴታቸውን ከፍ አድርገዋል የሚል ነው፡፡

የዳኝነት ችሎቱ፣ በማሴር፣ በኢንሹራንስ ማጭበርበር እና በውሸት የንግድ ሰነዶች ማዘጋጀት በቀረቡት ውንጀላዎች ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሏል፡፡

ጠቅላይ አቃቤ ህጓ ጄምስ ትራምፕ ፣ትራምፕ በኒውዮርክ ንግድ እንዳይሠሩ እገዳ እንዲጣልባቸውና ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ቅጣት እንዲወሰንባቸው እንደሚፈልጉ ተዘግቧል፡፡

የቀድሞው ፕሬዚደንት እና የሪፐብሊካን ፓርቲ የሚቀጥለው ዓመት፣ እ.አ.አ የ2024 ግንባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆኑት ትረምፕ ምንም አይነት ጥፋት አለመፈጸማቸውን እየተናገሩ ነው፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG