ቤጂንግ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ያለባት ሰሜን ኮሪያ፡ የኒዩክሌር ጦር መሳሪያ መርሃ ግብሯን ከማካሄድ እንድትገታ ታልመው ከተጣሉባት ማዕቀቦች የሚታደግ እገዛ እያደረግላችላት ስለ መሆኑ መጠኑ እየጨመረ የመጣ ማስረጃ መኖሩን አለም አቀፍ ምንጮች ይፋ አደረጉ።
በፒዮንግያንግ የኒዩክሌር ጦር መሳሪያ ሙከራ ጥረት ላይ የተጣለውን ማዕቀብ የደገፈችው ቻይና ተፈጻሚነቱን ተግባራዊ እያደረገች መሆኗን በመገልጽ፡ በተቃራኒው ሰሜን ኮርያን ታግዛለች’ የሚሉ አስተያየቶች አጥብቃ ስታጣጥል መቆየቷ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ቻይና በሰሜን ኮሪያውያን የኢንተርኔት ላይ ዘራፊዎች አማካኝነት የሚገኝ ገንዘብ ወደ ሕጋዊ ገንዘብነት የሚለውጡ ቻይናውያን ደላሎችን እንምደምትረዳ እና በተጨማሪም ማዕቀብ የተጣለበትን የሰሜን ኮርያን ሸቀጥ የቻይና መርከቦች ወደ ቻይና ወደቦች ማጓጓዝ መቀጠላቸውን አረጋግጠዋል።
መድረክ / ፎረም