በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተጫዋችዋን ያለፈቃዷ የሳሙት የስፔይን እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ከኃላፊነታቸው አልነሳም አሉ


በስተግራ የሚታዩት የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሉዊስ ሩቤለስ፣ ከዓለም ዋንጫው ድል በኃላ፣ ላ ሞንክሎአ ቤተመንግስት ውስጥ፣ ከስፔን ዋና አሰልጣኝ ጆርግ ቪልዳ ጎን ቆመው - ነሐሴ 22፣ 2023
በስተግራ የሚታዩት የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሉዊስ ሩቤለስ፣ ከዓለም ዋንጫው ድል በኃላ፣ ላ ሞንክሎአ ቤተመንግስት ውስጥ፣ ከስፔን ዋና አሰልጣኝ ጆርግ ቪልዳ ጎን ቆመው - ነሐሴ 22፣ 2023

የእንግሊዝን ቡድን ያሸነፈው የስፔይን የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ተጫዋችን ያለፈቃዷ ስመዋል የተባሉት የስፔይን እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ከኃላፊነታቸው እንደማይነሱ አስታወቁ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ይህን ያስታወቁት ከዓለም የሴቶች እግር ኳስ ጨዋታ ፍጻሜ በኋላ ደስታቸውን በሚገልጹበት ወቅት ተጫዋችዋን ያለ ፈቃዷ ከንፈሯ ላይ በመሳማቸው በተሰማው ቁጣ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የቀረበላቸው ግፊት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ነው፡፡

የፌዴረሽኑ ፕሬዚዳንት ሉዊስ ሩቤለስ ማድሪድ ውስጥ በአስቸኳይ ለተሰበሰበው የሬዴሬሽኑ ምክር ቤት “ከሥልጣኔ መልቀቅ አልፈልግም” ማለታቸውን አሶሴይትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ሩቤለስ ጂን ሄርሞሶ የተባለቸውን ተጫዋች ከንፈሯ ላይ የሳሙት አውስትራሊያ ውስጥ በተደረገው የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ በነበረው የሽልማት ስነሥርዓት ወቅት መሆኑ ተመልክቷል፡፡

ድርጊቱ ያስተከተለውን ቁጣ ተከትሎ በርካታ የስፔይን ዜና ማሰራጫዎች ሩቤለስ በገዛ ፈቃዳቸው ከሥልጣን ለመውረድ ማቀዳቸውን ሲዘግቡ ቆይተዋል፡፡

ሩቤለስ ግን ድርጊቱ በሄርሞሶ ፈቃድ “በስምምነት የተፈጸመ መሳሳም ነው” ብለዋል፡፡

ሄርሞሶ ከድርጊቱ በኃላ፣ ባላፈው እሁድ ባስተላለፈችው የቪዲዮ መልዕክት፣ ድርጊቱን “አልወደድኩትም ግን ደግሞ ምን ማድረግ እችላለሁ?” ብላለች።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG