በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በፍኖተ ሰላሙ ጥቃት ውዶቻቸውን ያጡ የከተማዋ ነዋሪዎች በቁጣ እና ቁጭት ውስጥ እንደኾኑ ገለፁ


በፍኖተ ሰላሙ ጥቃት ውዶቻቸውን ያጡ የከተማዋ ነዋሪዎች በቁጣ እና ቁጭት ውስጥ እንደኾኑ ገለፁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:57 0:00

በፍኖተ ሰላሙ ጥቃት ውዶቻቸውን ያጡ የከተማዋ ነዋሪዎች በቁጣ እና ቁጭት ውስጥ እንደኾኑ ገለፁ

ባለፈው እሑድ በተፈጸመ የከባድ መሣሪያ ጥቃት በርካታ ነዋሪዎቿን ያጣችው፣ በዐማራ ክልል የምዕራብ ጎጃም ዞን ከተማ - ፍኖተ ሰላም፣ ዛሬ መጠነኛ መረጋጋት ቢታይባትም፣ በደረሰው ሰብአዊ ጉዳት፣ ቁጣ እና ቁጭት እንዳሳደረባቸው፣ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፡፡

በጥቃቱ ቆስለው በሕክምና ላይ ከሚገኙ ነዋሪዎች፣ ከጉዳታቸው የተነሣ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች አስከሬን፣ በዛሬው ዕለትም ከሆስፒታል ሲወጣ እንደተመለከቱ፣ አክለው ተናግረዋል።

በተመሳሳይ፣ ከፍኖተ ሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው የቡሬ ከተማም፣ ትላንት ከቀትር በኋላ እና ዛሬ፣ አንጻራዊ ሰላም በመገኘቱ፣ የሞቱ ሰዎችን እየቀበሩ እንደኾነ፣ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል። ወደ ሁለቱም ከተሞች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጸጥታ ኃይል እንደገባም ጠቁመዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG