በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዋጋ ንረቱን መቋቋም የተሳናቸው ነዋሪዎች


የዋጋ ንረቱን መቋቋም የተሳናቸው ነዋሪዎች
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:53 0:00

የዋጋ ንረቱን መቋቋም የተሳናቸው ነዋሪዎች

የኑሮ ውድነት፣ ከቀን ወደ ቀን ፈተና እየኾነባቸው እንደሚገኝ፣ በዐዲስ አበባ ከተማ፣ አስተያየታቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የሰጡ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ መንግሥት፣ የዋጋ ንረቱን ሊያቃልሉ የሚችሉ ርምጃዎችን እንዲወስድም ተማፅነዋል፡፡

የዋጋ ንረት፣ የመላው ዓለም ፈተና እንደኾነ፣ ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የገለጹት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ንረት፣ መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡

መንግሥት፣ የቀጣዩን ዓመት በጀት ያዘጋጀው፣ የዋጋ ንረትን ሊቀንስ በሚችል መንገድ እንደኾነም አብራርተዋል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ የምጣኔ ሀብት ባለሞያ እና ተንታኝ ዶር. ቆስጠንጢኖስ በርሄ ግን፣ መንግሥት በገበያው ላይ የሚኖረውን የገንዘብ መጠን ከመቀነስ ጀምሮ፣ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር መውሰድ ያለበትን ርምጃ ጠቁመዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG