በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ሱዳን ወደለየለት የእርስ በእርስ ጦርነት እየገባች ነው” ጉቴሬዝ


ፋይል - በሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ግጭት በቀጠለበት ወቅት በሱዳን፣ ካርቱም ጭስ ሲወጣ ይታያል። ሰኔ 8፣ 2023
ፋይል - በሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ግጭት በቀጠለበት ወቅት በሱዳን፣ ካርቱም ጭስ ሲወጣ ይታያል። ሰኔ 8፣ 2023
  • የኢጋድ መሪዎች አዲስ አበባ ላይ እየመከሩ ነው

በሱዳን ያለው ግጭት ሙሉ ለሙሉ ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እያመራ መሆኑ እና ይህም ቀጠናውን ወደ ትርምስ ሊወስድ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አስጠንቅቀዋል።

ዋና ጸሃፊው አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ትናንት ማስጠንቀቂያውን የሰጡት ቅዳሜ ዕለት በተፈጸመ የአየር ጥቃት 22 ሲቪሎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን ተከትሎ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ 3ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ጦርነት የሚቆምበትን መላ ለመሻት፣ የኢጋድ አባላት የሆኑት የኢትዮጵያ፣ ኬን ያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን መሪዎች፣ የልማት በይነ መንግስታቱ ጉዳዩን እንዲከታተሉ በሰጣቸው ሃላፊነት መሠረት በጉዳዩ ላይ ሊመክሩ አዲስ አበባ ላይ ዛሬ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል።

የቅዳሜው የአየር ጥቃት የካርቱም እህት ከተማ በሆነችው ኦምዱርማን እንደደረሰ ሲታወቅ፣ ትናንት እሁድም በካርቱም በሚገኘው የፕሬዝደንቱ ቤ/መንግስት አካባቢ እና በኦምዱርማን ተፈጽሞ እንደነበር የዓይን ምስክሮችን ጠቅሶ የኤኤፍፒ ዜና ወኪል ዘግቧል።

ጉቴሬዝ የአየር ጥቃቶቹን ማውገዛቸውን ምክትል ቃል አቀባያቸው የሆኑት ፋርሃን ሃቅ አስታውቀዋል።

ሁለቱ ተፋላሚ ጄኔራሎች፣ የጦር ሠራዊቱ አዛዥ የሆኑት አብደል ፋታህ አል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ አዛዥ ሞሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ በስብሰባው ላይ እንዲገኙ ቢጋበዙም አለመገኘታቸው ታውቋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG