በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኬንያ አል-ሻባብ ያደረሰው ከተባለ ጥቃት ተከትሎ 20 ታጣቂዎች ተገደሉ


ፎቶ ፋይል፦ ናይሮቢ፣ ኬንያ
ፎቶ ፋይል፦ ናይሮቢ፣ ኬንያ

ኬንያን ከሶማሊያ በሚያዋስነው በማንዴራ አካባቢ ትናንት ረቡዕ አልሻባብ ያደረሰው ከተባለ ጥቃት ተከትሎ 20 ታጣቂዎች መገደላቸውን እና 8 ፖሊሶች መጎዳታቸውን የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ኃይል አስታውቋል።

የልዩ ፖሊስ አባላት በማንዴራ አካባቢ ቅኝት በማድረግ ላይ ሳሉ፣ በደፈጣ ከባድ ተኩስ እንደተከፈተባቸው ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል። ከባድ መሣሪያዎች መውረሱንም አስታውቋል።

ከአል-ቃይዳ ጋር ግንኙነት ባለው በአል-ሸባብ በርካታ ጥቃቶች መፈጸሙ ለረጅም ግዜ ተዘግቶ የቆየውን ሁለቱን አገራት የሚያገናኘውን መንገድ እንደገና የመክፈቱን ጉዳይ እንዳዘገየው የኬንያ መንግስት በትናንትናው ዕለት አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG