በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የትግራይ ተዋጊዎች 85 በመቶ ትጥቅ እንደፈቱና አደረጃጀታቸውን ማፍረሱም በኵሓ መጀመሩ ተገለጸ


የትግራይ ተዋጊዎች 85 በመቶ ትጥቅ እንደፈቱና አደረጃጀታቸውን ማፍረሱም በኵሓ መጀመሩ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:25 0:00

የትግራይ ተዋጊዎች 85 በመቶ ትጥቅ እንደፈቱና አደረጃጀታቸውን ማፍረሱም በኵሓ መጀመሩ ተገለጸ

በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶርያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል በተደረገው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ በትግራይ ክልል የሚገኙ ተዋጊዎች፣ 85 በመቶ የጦር መሣሪያቸውን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማስረከባቸው ተገለጸ።

ዛሬ፣ በመቐለ ከተማ በተከናወነው ቀጣይ የርክክብ ሥነ ሥርዐት ላይ፣ የአፍሪካ ኅብረት ያቋቋመው፣ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት ክትትል እና ቁጥጥር ቡድን በታዛቢነት ተገኝቷል።

በሰላም ስምምነቱ መሠረት፣ የትጥቅ ማስፈታቱን ተከትሎ የሚከናወነው፣ የተዋጊዎችን አደረጃጀት የማፍረስ ሒደት፣ በዛሬው ዕለት፣ በመቐለ ዙሪያ በምትገኘው ኵሓ መንደር፣ በታዛቢዎች ፊት በኦፊሴል መጀመሩ ተገልጿል፡፡

XS
SM
MD
LG