በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በማዕከላዊ ሶማልያ 219ሺሕ ሰዎች በጎርፍ ተፈናቀሉ


በሶማሊያ ባልደወይን ከተማ በደረሰው የጎርፍ ውሃ ውስጥ ሴቶች ሲሄዱ ይታያሉ። የሸበሌ ወንዝ ሞልቶ በመፍሰሱ የደረሰው ጎርፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ቤታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እንዳደረጋቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) አስታውቋል።
በሶማሊያ ባልደወይን ከተማ በደረሰው የጎርፍ ውሃ ውስጥ ሴቶች ሲሄዱ ይታያሉ። የሸበሌ ወንዝ ሞልቶ በመፍሰሱ የደረሰው ጎርፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ቤታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እንዳደረጋቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) አስታውቋል።

በማዕከላዊ ሶማልያ በለደወይን ከተማ፣ የሸበሌ ወንዝ ሞልቶ አካባቢውን በማጥለቅለቁ፣ 219ሺሕ ሰዎች ሲፈናቀሉ፣ ጎርፉ እና የወንዝ ሙላቱ በአጠቃላይ 460ሺሕ ሰዎችን ለችግር መዳረጉ ተነግሯል፡፡

እንደ አሶሺዬትድ ፕረስ ዘገባ ከኾነ፣ ጎርፉ በበለደወይን ከተማ የሚገኙ የመንግሥት ቢሮዎችን ጨምሮ ሌሎችም አገልግሎቶች እንዲዘጉ አስገድዷል።
የጎርፍ አደጋው፣ በታሪክ በአካባቢው ያልታየ መኾኑን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች በመናገር ላይ ናቸው።

በለደወይን የተሰኘችው ከተማ፣ በክልሉ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ እንደሚኖርባት ተመልክቷል።

የጎርፉ አደጋ የተከሠተው፣ በተከታታይ ዓመታት ድርቅ ምክንያት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሶማልያውያን፣ ለረኀብ በተጋለጡበትና አገሪቱ ከእስላማዊ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋራ በመዋጋት ላይ ባለችበት ወቅት ነው፡፡

XS
SM
MD
LG